Friday, March 15, 2013

ጸሊም …..

ኑሮዬ ከተወለድሁበት እትብቴ ከተቀበረበት መንደር ሰፈር ቀዬ በጣም ሩቅ ነው። ያባት ያያቴ አህያ ረግጦት በማያውቅ የሰው ሀገር። ምናልባት እንደ ቡድሃወች እና እንደ ሂንዱዎች እምነትና እሳቤ ነፍሳት ደግመው ደጋግመው አፈር ለብሰው እና ልሰው ቢወለዱ እንኳን ያባት ያያት የቅመአያቶቸ አህዮች አሁን በምኖርበት ሀገር አንድም ግዜ ስንኳ ተወልደው አገሩን ሰርዶ ግጠውበታል ብዬ አላምንም፤ አላስብምም፤ያለዚያማ እነሱ ጠልተውት ባባቶቼ ባድማ ከተወለዱ፣ በፍጥረት ላዕላይ ያለሁት ፍጡር እኔ እንደምንስ ብዬ ላየው እና ልኖርበት አስብና እመኝ ነበር?!…..

እንግዲህ ኑሮዬ በባዕድ ሀገር ቢሆንም ላንድ የተቀደሰ/የተደጎሰ ምግባር ባለቃችን ፈቃድ ለትውልድ አገሬ ሰፈር መንደሬ ወደሚቀርብ አገር ሄድን። መዳረሻችን ግን በፊትም አሁንም ወደፊትም ሳስበውቅርጽ ያለው መንገድን የተከተለ ነው። ከዚያም እትብቴን ብሻው ብዬ ሳስብ የትውልድ ቀዬዬ ልክ የመሰለ መንገድን መከተል ነው። ከዛም ከች ነው….

መሄድን ተመኘሁ። መንጎድ አማረኝ። እሽክም ማለት።…… ነጎድሁ፣ ወደትውልድ ቀዬዬ።……….

በአካልም በመንፈስም  መራቄን፣ መለዬቴን የተረዳሁት ግን አንዱንም ሁነት ሳላውቅ ይህን ያህል ዘመን በመኖሬ ነው።
እናትና አባቴ ተለያይተዋል። ለኔ መርዶ ይሁን ምን፤ እውን ይሁን ህልም አላውቅም። ግን መሆኑን ከእህት ወንድሞቼ ተነገረኝ። አባቴ ወደከተማ ጠጋ ብሎ ብዙዎችን እህትና ወንድሞቼን ሰብስቦ ይኖራል። አላገባም። ከብቶች ያረባል። ጥሩ የወተት ምርት እና ትንሽም የንባብ መጻህፍትን እየነገደ የተሻለ የተባለ ኑሮ ይኖራል። ስለኑሮው ስጠይቃቸው እህቶቼ እና ወንድሞቼ የመለሱልኝ ነው። ታላቋ እህቴ ግን አሁንም እርጥቡን ከደረቅ ማግዳ እንጀራ ልትጋግር ደፋ ቀና ትላለች። እሳቱ አልነድ ብሎ አስሸግሯታል።…. ኑሮ….. በዚህም ውስጥ ያች የተረገመች ነፍስ ከስጋ ውሻቅ ውስጥ እድሜዋን ታራዝም ዘንድ ትፍገመገማለች። ያለዚያማ ምግብ ለምን ያስፈልግ ነበር? እርጥብ ከደረቅ ማግዶ በእንጀራ ስም እንደጃርት በጢስ መታፈን፣ የነፍስን የኃጥያት እና መርገምት የፍዳ ቅጣትን ዘመን ከመጨረስ በማይለዬ የኑሮ ማጥ ውስጥ የተለዬ ፋይዳ የተለዬስ ትርጉም ሊኖረው ይሆን?

እናቴ ግን ራቅ ወዳለ ቦታ ሄዳ ሌላ ባል እንዳገባች ሰማሁ። የቤተሰቡን የመጨረሻ ልጅ ይዛ። ማወቅ ፈለግሁ። በጣም። ነገሮች ሁሉ ተደናገሩኝ።…. ሁሉን ማወቅ ፈለግሁኝ። ሁሉንም። ጥያቄዎች ያለወረፋ ተጋፍተው መጡ። ካንደበቴ ግን አንዱም መውጣት አልቻለም…. በጣም ይጋፋሉ እና ነው። በዚህ መሃል ከእንቅልፌ ስነቃ፣ ሰውነቴ ድቅቅ ብሏል። አንድም መገጣጠሚያ በጅማት የተቋጠረ አይመስልም፣ ስነሳ የተሰማኝ ስሜት። ይህ ሁነት ህልም ቢሆንም ይህን ያሳዬኝን እንቅልፍ አይጠሉ ጠላሁት። በቃ ጠላሁት። አቅለሸለሸኝ። ይህን ያሳዬኝንም ጸለምተኛ አስተሳሰብ የተሸከመ ጭንቅላቴን ቆርጦ መጣል አሰኘኘ። ራሴን ጠላሁት። ረገምሁት።

ፍጹም ጸለምተኛ አስተሳሰብ….  

የላስታ ላሊበላ፣ የዋግ የሰቆጣ የራያ …. ወሎ፣ጎንደር ጎጃም እያልሁ በባህል ዘፈን መርገፍ ያዝሁመርገፍገፍ። ይህ የመርግ ያህል የተሰማኝ ትኩስ የህልም ስሜት ቅልል እስኪልልኝ። እንግዲያው ጸሎትስ አልሻም። ይህን ያሳዬኝ ሴጣን ነው አልልም እና። እናም ቅልል አለኝ። ይህን የባህል ጭፈራ ስለጨፈርሁም እናቴን ያከበርኋት፤ የካስኋትም ያህል ተሰማኝ። ግን ቢራ አምሮኛል፤ እንዳማረኝም እስካሁን አልጠጣሁም። ለክፏዋ ስሜት ብክንክን እንግብግብ ለምታደርገዋ የመበደል እና የበዳይ ስሜት ማስረሻ ማስታገሻዋ ያችው ውብ የወይንጠጅ ናትና ነው…..

(March 15, 2013)

የፍቅር ስፌት ትችይ ይሆን?

ፍቅሬ ሆይ
የፍቅር ስፌት ትችይ ይሆን?
ማንቃት ግራምጣውን
ባለላ አስጊጦ?
መሰበዝ ሰበዙን?
ወንድ ነኝ እና ውጥኑን ልወጥን
ከቻልሽ መቋጨቱን
ማሳመር ስፌቱን፤
ግራምጣ አንቅቶ
አለላ አልሎ.....
አክርማውን ነቅለሽ ሰበዙን ከሰበዝሽ
ፍቅር መስፋት ከቻልሽ፤ በወስፌ እዬወጋሽ
ግድ የለሽም ለውጥኑ
በወንድነት እኔው ልወጥን
መቀልበሱን ግን አደራ ላንች
በሴትነት ውጥኑን መቋጨቱን።

Z.K. /March 15, 2013

Thursday, March 14, 2013

ፍቅሬን ታደግኋት….




አንድ ትልቅ ሱቅ ውስጥ ገባ ስል ምግብም ይሸጣል። የረሃብ ስሜት አለብኝ ግን ምን ዓይነት ምግብ መብላት እንዳለብኝ አልወሰንሁም ብቻ ሳይሆን አላውቅም… ፈረንጅኛ ይመስለኛል። ማለቴ ፈጥኖ ደራሽ ነገር…. ሴትዮዋ የሆነ ነገር ጠቅልላ ሰጠችኝ። እኔም ፳ የብር ኖት ሰጠኋት። ዋጋው ፪ ብር ነው ብላ ፲ የብር ኖት ሰጥታኝ ቀሪውን ፰ ብር ለማምጣት ወደብር ሳጥኗ ሄዳ በዚያው እልም አለች። በቃ ቀረች…. የ፪ ብር ምግብ በልቼ ፰ ብር tip የምገፈትር ምስኪን ደሃ ማለት እኔ ሆንሁ። ደግሞ ጨምራ የሰጠችኝ ቸኮላት መሳይ ነገር በጣም ይመርራል፤ ግን ቸኮላት ነው በማለት በላሁት። የታባቱንና… የቅል ፍሬ አሽትቸ ያደግሁ ልጅ እንኳን ምግብ ነው ብለውኝ ገና ለገና ቡዳ እንዳይበላኝ ስንት ነገር አድርጌ ያደግሁ የጉድ ነኝ።

ከበሩ ልወጣ ስል አንድ ለረጅም ግዜ የተለየሁትን እና አሁን አካሉ በጣም ጠብደል የሆነ ጓደኛዬን እና በናቴ በኩል የሚዘመደኝን ዘመድ አገኘሁት። ጥቂት አወራን። እርሱም እንደኔ ያለም ገዣችን የሆነውን ሆዱን ሊደልል ነው ጎራ ያለው። እርሱ ምግብ ሊያዝዝ ወደጥግ ሲሄድ እኔ ወጣ አልሁ። ውጭው በሚያምር መልኩ ባረንጓዴነት ያጌጠ ነው። የሙሪኝ ሳር ነው ግቢውን የሸፈነው። አንዳንድ የማውቃቸው ተማሪዎችን ከርቀት ቆሜ አስተውል ጀመር። ያ ዘመዴ ግን ብቅ አልል አለኝ። ጠበቅሁት ጠበቅሁት… ብቅም አላለ። ትቸው ሄድሁ። በዚህ አጋጣሚ ይቅርታ ብየሀለሁ።

አመጣጤ ለምን ነበር እዚህ ቤት? …. አወ ፍቅሬ እዚሁ ስለምትሰራ ነው። ባለሁለት ፎቅ ነው እና የስራው ቦታ፤ ከላይኛው ወለል እየሰራች ነበር፤ ወርዳ ልታናግረኝ ግን ፈቃደኛ አይደለችም (ቢያንስ አትመስልም ነበር)። ይመችሽ… አልተቀየምሁሽም ውዴ። እኔ እንደሆንሁ አልፈልግህም የሚል ቃል ካልሰማሁ በቀር ዘውገኛ ነገር አይፈልጠኝም። ስትተይኝ ግን አደራሽን የመለየት ገመዱን እንዳታስረዝሚው…. ባልፈለግሽበት በዚያች ሰዐት አልፈልግህም በይኝ። ያልዚያ ግን ሄድ መጣ አበዛለሁ። አሁንም የኔ እንደሆንሽ አስባለሁና።

አሁን መንጎድ ጀምሪያለሁ። ዘመዴ በዚያው የውሃ ሽታ ሆኗል እና። እግረ አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ ያጎቴን ልጅ እና የናቷን እህቶች እና የእህት ልጆች በመንገዴ ፊለፊት እንደኔው ሲነጉዱ ከርቀት አየኋቸው። ፈጥኘ ለመድረስ ሁለቱን ባንድ መራመድ ጀመረሁ። ከፊለፊት ግን አቀበት ብቻ ሳይሆን ደረጃ መሰለም ነው። እነርሱ በጨዋታ ሲያዘግሙበት እኔ ጭራዬን ነው የቆለፍሁበት እና ልክ አቀበቱን ወጥተን ደልዳላው ቦታ ስንደርስ ተቀላቀልኋቸው እና የአብሮአደግ እና የህትነት የወንድምነት ሰላምታችን እና መሳሳማችንን ከውነን ስንጨርስ ከመሃላቸው አንዲት የማላውቃትን ልጅ በጨረፍታ አየት አድርጌ ይህች ጉብል ደግሞ የማናት? ስል…. ልብህን ሰብስብ ተባልሁ። እኔ እንኳን ባለማወቅ ነበር የጠየቅሁ። እነርሱ ደግሞ ጫጩት ፈላጊ ጩልሊት አደረጉኝ። አይ no ካሁን በፊት አይቻት የማላውቅ ስለሆነ የማ ልጅ ናት ብዬ ነው አልሁኝ። በውነቱ በጣም ቆንጆ ናት። ከውዴ ግን አትበልጥም። ማንነቷ ተነገረኝ። አገዳደሟ ወደየት ነው ስል ካገር ውጭ እንደምትኖር እና አሁን ወደናዝሬት ልትሄድ ሶስት ወጠምሻዎች (ሶስቱም ጓደኞቼ ናቸው) በመኪና ሊያሳፍሯት እንደሆነ ተነገረኝ።…. እንግዲህ የደራ የቤተዘመድ ወሬያችንን እየኮመኮምን መንገዳችንን ቀጠልን፤ ወደቤተሰቦቻችን። በዚህ መሃል ያጎቴ ልጅ እንዲህ ስትል ጠየቀችኝ፤ እንዴት ነው ልብህ ምን አሰበ? እኔ ደግሞ በምኑ? አልሁ። በጉብሊቷ? አለች እርሷ። ልቤን ለሌላ ከሸጥሁት እኮ ቆዬ አልኋት።…. በልቤም ውዴ ሆይ ፍቅርሽን ታደግሁት አልኋት። መንገዳችን እንደቀጠለ ነው። መምሸትም ጀምሯል። ቤታችን ሳንደርስ ግን ከንቅልፌ ነቃሁ።

ዛሬ ፍቅሬን ታደግኋት።


አጭር ህልምወለድ/March 15, 2013

Wednesday, March 13, 2013

Racism, Personified God, Universal Feeling and Evolution

"Albert Einstein calls God the 'universal feeling,' not the personified one, who is accountable for racial, narrow-mindedness and genocidial crimes.”
 


First of all I would like to thank a facebook friend for sharing the above quote.

My take on this view is as follows. It however depends on the agreement on the definition of "scientific fact" and taking evolution as a scientific fact (and theory).

Scientific fact as a fact perceived by the five senses of the human body, and things whose variable properties are measured differentially with respect to a chosen characterising and preselected defining variable with high throughput and reproducibility regalrdelss of the observer in different places and at different times is a scientific fact. In this regard evolution is a scientifc theory that bases on scientific fact. Accordingly, every object is a spec of dust, where in time after the great bang a form of exsitence of a collection of dust gave rise to what is called "living things" with certain characteristic properties. Over the ages, they reproduced, multiplied and gave varieties up to homosapiens of us. Though not clear yet where and how the first biochemical stuff started and how and why it started, the general 'scientific' consensus is that information encoded in the great biochemical stuff called RNA or DNA is passed on to generations along the way to this date. A slight difference in the encoded information, and the environmental stress lead to expression of one specific set over the other or otherwise leads to extincition. This has given rise to the "formation" of different varieties of "living things". It happens in such a long time that it is called evolution, and not revolution. In this regard we humans are also product of evolution - evolved from a primitive species in relation to coping up the external environmental forces.

That being said, I think that being racist and narrow-mindedness are purely evolutionary - a way of self-defending to surviving and being eternal by passing on our genetic information. Well, if not completely true that is what the current scientific evidence seems indicating. In this strange and enormously unknown world (whereby we live our days in probability), there is a great sense of fear of self-extinction that we have to fight hard to live and that in turn also leads to killing other fellow humans (an element of genocidal crimes).

Then, either we misunderstood God or there is no such thing called God but is only the product of the human thought - a way of expressing the fear of losing life, is only mere reason to be considered as a factor for those inhumane qualities. There are a number of state-waged war cases whose causes are religion (or at least scriptural). Saying my God is the one and only God, or at least saying "mine is better than yours" and fighting for this to death is no different from fighting to protect the throne of a king; I mean that God is no worth of worshiping as s/he is not self-defending by his/her own mighty.

I also don't agree with the definition/calling "universal feeling." How come we give a thing universality while our definitions or callings are based on our understanding, which is dynamic itself? If we say it is a feeling that every human of all the time shall feel and have the access to feel (so to call universal) is simply denying evolution.

As a final out to my talk, this peice is not to show that evolution is true, and no religion is valid. It rather is to argue that it is not the personified God that is a cause to all inhumane deeds, and as to Eisntein, who I think is a high profile scietist who accepts evolution as a solid and solid fact, saying God as a "universal feeling" is simply self-refuting the very idea of evolution where the conclusion of "no peronifed God" is based. In evolution there shall exist no universality; everything is dyanamic and relative. Maybe time is eternal, and it would be if time itself is for real.